በደብረብርሃን ዩኒቨርስቲ ተማሪወች የነፃነት ትግል ፅሁፎች በት/ቤት ሰሌዳወች ላይ እየፃፉ ነው፤ የሌሎች ዩኒቨርስቲወች ተማሪወች ሁለገብ የትግል ንቅናቄውን እንዲቀላቀሉ ጥሪ ቀርቧል።በት/ቤት ሰሌዳወች ላይ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ፣ አርበኞች ግንቦት 7፣ አንድ ኢትዩጲያ የሚሉ ፁሁፎች እየተፃፋ ሲሆን በእነዚህ ፁሁፎች ብቻ አስተማሪወችና የህወሓት ቅጥረኛ ጆሮጠቢወች፣ የት/ቤቱ የህወሓት/ወያኔ አስተዳደር ክፋኛ መረበሻቸው ታውቋል።” የፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ህልም እውን ይሆናል!” “የመሪያችንን ትዕዛዝ ለማስፈፀም ለነፃነት እስከሞት!!” በማለት የነፃነት ትግሉን እያቀጣጠሉ ያሉት ተማሪወች በመላ ኢትዩጲያ ዩኒቨርስቲወች ነፃነት ፈላጊ ተማሪወች የሚቀጣጠል ትግል እንደጀመሩ ይናገራሉ።የወያኔ ሰላዩች እንደሚከታተሉን እኛም በትክክል እየተከታተልናቸው እንገኛለን የህቡዕ ቡድኑን መዋቅር በማስፋት ትግላችን መልኩን እየቀየረ በእብሪት ጥጋብ ልቡን ያሳበጠውን የወያኔ ወንበዴ ቡድን መቆሚያ መቀመጫ በማሳጣትና እንዳይረጋጋ አድርጎ በመረበሽ ለነፃነት እስከህይወት መስዋዕትነት የደረሰ ትግል በአንድነት አድርገን ነፃነታችንን እንቀዳጃለን በማለት ሁሉም በተግባር ለነፃነት እንዲነሳ ጥሪ ያስተላልፈዋል።
Advertisements