ዛሬ የካቲት 19/2010 የአሜሪካ ኢምባሲ በራዲሰን ሆቴል ለአንዱአለምና አራጌና ለእስክንድር ነጋ የምሳ ግብዣ አደረገላቸው!!
በዚህ የምሳ ግብዣ ላይ ከአሜሪካ ሀገር ወደ ኢትዮጵያ የመጡ ሶስት (3) ሰዎች አንዱአለምንና እስክንድር ያናገሩዋቸው ሲሆን፣ አንደኛዋ ሜሪላንድ ውስጥ ካምብሪጅ የምትባል ከተማ ከንቲባ መሆናቸው ታውቋል። ሁለቱ ግለሰቦች ደግሞ አክቪስቶች ናቸው። በውይይታቸው፣ በብሄራዊ እርቅ ዙሪያ ሰፊ ውይይት ማድረጋቸውን ከስፍራው የደረሰኝ ዜና ያስረዳል።
ችግሮችን በሰላማዊ መንገድና በውይይት መፍታት እንደሚያስልፈግ መነጋገራቸውንና፣ በዚህ ንግግር ላይ ከኢምባሲው ባለስልጣናት የተወከሉ ተጨማሪ ሶስት ሰዎች መገኘታቸው ታውቋል። ሶስቱ ሃላፊዎች የፖለቲካ ክፍልና የፕሬስ ክፍል ባለስልጣናት ሲሆኑ፣በቀጣይም ከኢምባሲው ካሉ ኅላፊዎች ጋር ተጨማሪ ንግግር ለማድረግ ቀጠሮ ይዘው መለያየታቸውን ለማወቅ ተችሏል።
Advertisements